ብርቱካን በቃሊቲ - አቶ ኃይሉና አቶ መለስ ተጨባበጡ

ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

ትዝ ይለኛል ከሁለት ዓመታት በፊት ከአንድ ኢህአዲግን ከሚደግፍ ወዳጄ ጋር የተነጋገርኩት። የቅንጅት መሪዎች ከእሥር ቤት ተፈተዋል። ወደ ሁለተኛው ሚሊንየም ለመሸጋገር እየተዘጋጀን ነው። አቶ መለስ ዜናዊ፣ ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ አቶ ስዩም መስፍን … ሁሉም በአንድ ላይ ጎን ለጎን ቆመው፣ እንደ ወንድማማቾች፣ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሠላም፣ የፍቅር፣ የእርቅና የአንድነት መልዕክት በቴሌቭዥን ቢያሰሙን በጣም ጥሩ ይሆን እንደነበረ ለዚሁ ወዳጄ ገልጬለት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከግንቦት ሰባት ወዲህ፡ ከግንቦት ሰባት ወዲያ

አለቃ ተክሌ-ከካናዳ (ክፍል ሁለት)


ምን ላይ ነር ያቆምኩት? የትግራይ ጉዳይ ላይ። ከዚያ በፊት ግን፡ ማለትም የጀመርኩትን የሚኮሰኩስም የሚለሰልስም፤ ወደድንም ጠላንም ግን ልናመልጠው የማንችለውን ርእስ ከመቋጨቴ በፊት ትንሽ እንቀልዳለን። (በነገራችን ላይ፡ ከዳላስ ወደ ሲያትል በሚጓዘው የአሜሪካን አየርመስመር (አ.አ.) ላይ ሆኜ ነው ይሄንን ጽሁፍ የማስተካክልላችሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከግንቦት ሰባት ወዲህ፡ ከግንቦት ሰባት ወዲያ

አለቃ ተክሌ-ከካናዳ (ክፍል አንድ)

ትንሽ ወደኋላ፡ ሌላ ዙር ቅስቀሳ

ቅስቀሳ እወዳለሁ። “ይሄ ቅስቀሳ አይደለም ቁስቆሳ ነው። ለነገሩ አብላጫው ዝምተኛ፡ ያንተን ቅስቀሳ የሚያነብ አይደለም፡ ዝም ብለህ ነው የምትደክመው” የሚል ቀስቃሽና ቀዥቃዥ አስተያየት ደርሶኝ ነበር፡ ሰሞኑን። ስለዚህ በግንቦት ሰባት የዳላስ ስብሰባ ላይ ያቀረብኩትን አንድ የቁስቆሳ ጽሁፍ እንደምለጥፍላችሁ የገባሁትን ቃል አጥፌ፡ ትንሽ ቆየሁ። ግን ሰው መቀስቀስ ባልችል ለምን ራሴን አልቀሰቅስም የሚል ቅስቀሳ ቀሰቀሰኝና፡ ይኸው ጽሁፌን፡ እናንተን ለመቀስቀስ ሳይሆን ራሴን ለመቀስቀስ ሰድጄዋለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2002 ምርጫና ቻቻታው (ኩችዬ)

ኩችዬ http://www.kuchiye.blogspot.com/

ከ2002 ዓ.ም. ምርጫ ጋር በተያያዘ ፊት-ለፊትና በሠያፍ የሚወረወሩት ትችቶች ብዛታቸውም ግለታቸውም እየጨመረ መሄዱ በመሃላችን የሰፈነውን የመረበሽና የጥርጣሬ ስሜት ያመለክታል። ስጋቱ ማንንም ከማን የለየ አይደለምና ትንሽ ልተችበት ፈለግሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ምርጫማ ጥሩ ነው” መክብብ ማሞ

መክብብ ማሞ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

… የቅንጅት ሕጋዊ ወራሽ ነኝ የሚለው አንድነት ፓርቲ መድረክን ከመሠረቱ ስምንት ፓርቲዎች መካከል አንዱ ነው። በአጀማመሩ የቅንጅትን ስትራቴጂ እየተከተለ ያለው መድረክ በዚህ አካሄዱ ከቀጠለ በመጪው ምርጫ የመሳተፍ አዝማሚያ ይታይበታል። በተለይ ባለፈው 1997 ምርጫ ከተቃዋሚው ጎራ ያልነበሩ አዳዲሶቹ የመድረክ አባላት በዚህኛው ምርጫ ዕድላቸውን የመሞከር ፍላጎት እንዳላቸው ፍንጮች ይታያሉ። መድረክ ከተሳተፈ ደግሞ አንድነት ፓርቲም እንደአባልነቱ መሳተፉ የማይቀር ይሆናል። ይህ ከሆነ ደግሞ አቶ አስራት “የብርቱካን ጉዳይ በምርጫው ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታ አይሆንም” ያሉት ትክክል ነው ማለት ነው። ስለዚህ ዶ/ር ኃይሉ የሰጡት ማስተባበያ ተቀባይነት አይኖረውም፤ በመሆኑም አንድነት ፓርቲ የወ/ት ብርቱካንን መፈታት በምርጫ ለመሳተፍ እንደ ቅድመ ሁኔታ ሳያቀርብ በምርጫው ይሳተፋል ማለት። ይዘገንናል!! …

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዲግ ለምን ብርቱካን ሚደቅሳን ይፈታል? (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ (ጥቅምት 3 ቀን 2002 ዓ.ም.) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

በዚህ በያዝነው የኢትዮጵያ አዲሱ ዓመት (2002 ዓ.ም.) የሚካሄደውን ምርጫ በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አቶ አሥራት ጣሴ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ዙሪያ የሰጡት ቃለ መጠይቅ ትንሽ እሳትን እንደለኮሰ እያየን ነው። (ኢንጂነር ግዛቸው እሳቱን ለማጥፋት ቢሞክሩም)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መሪውን ያላስፈታ ፓርቲ አዝማች እንደሌለው ጦር ይቆጠራል

ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)

"... ገዢው መንግሥት ሥልጣን ሲለቅ ተቀናቃኝ የነበሩ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱማ ማንም የሚያውቀውና ባለፉት ሁለት መንግሥታት መለዋወጥም አይተነዋል። አሳሪውን መንግሥት በምርጫ ከሥልጣን ስናስወግደው ያኔ የብርቱካን ነፃነትም ይከበራል ብሎ መናገር ወያኔ እስከሚወርድ ድረስ ብርቱካን በእስር የመቆየቷን ጉዳይ አምኖ እንደመቀበልም ይቆጠራል። ከዚህም ባሻገር የዕድሜ ልክ እስራቱንም ቢሆን እንደመቀበል ይመስላል። ይህ መግለጫ በተለይ ከራሷ ፓርቲ አንደበት መውጣቱ በእጅጉ ያሳፍራል። ..."

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ካለፉ ትብብሮች - ለትምህረት (አሸብር)

አሸብር (ከጀርመን)

“እርስ በርሳችሁ ስትተራመሱ የወያኔን አንድ ዝንብ እንኳን ‘እሽ‘ ሳትሉ ዕድሜአችሁን ገፋችሁ“ ከታዛቢ

በአሁኑ ጊዜ የተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጀቶች ስለሕብረት ጉዳይ ሲወያዩ፤ አልፎ - አልፎ የሚያነሱት ጉዳይ ካለፉት ትብብሮች ምን መማር እንዳለባቸው ነው። ስለሆነም ካለፉ ትብብሮች ሊገኝ ስለሚችል ትምህርት አጋጣሚ ያስገኘልኝን ግንዛቤ ባካፍል በጥቂቱም ቢሆን አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብዬ ስለገመትኩ የምትከተለዋን ለማለት ሞክሬአለሁ። በቅድሚያ ግን አንባቢዎችን ማሳሰብ የምሻው፤ የጽሑፌ ዓላማ በየጊዜው የተቋቋሙ ሕብረቶች ውስጥ በእኔ ዕይታ ለጋራ ትግሉ እንቅፋቶች ነበሩ ያልኳቸውን ድርጊቶች ለማሳየትና ለወደፊት ትምህርት የሚቀሰምባቸው ይሆናሉ በሚል ብቻ እንጂ፤ ባለፉት ለተፈጸሙ ልማቶችም ሆኑ ጥፋቶች ማንንም ተጠያቂ አድርጎ ለማቅረብ የታሰበ እንዳልሆነ ነው። ስለዚህም በጽሑፌ ውስት በክፉም ሆነ በደግ የማንንም ግለሰብ ሆነ ድርጅት ስም አላነሳሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ ሊደገፍ ይገባዋል - ኢትዮጵያዊነትን ያንጸባረቀ ነውና (አማኑኤል ዘሠላም)

አማኑኤል ዘሠላም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ከሦስት ዓመት በፊት ወደነበረው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ለትውስታ ያህል ልመልሳችሁ። ተቀማጭነታቸው አሜሪካን ሀገር የሆኑ፣ የቀድሞ የሰሜን አሜሪካ የቅንጅት ድጋፍ ማኅበር ጥቂት አመራር አባላት፣ በሆላንድ ሀገር ከኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር፣ ከኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር፣ ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና ከሲዳማ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር ጋር ትብብር ለነፃነትና ለዲሞክራሲ (ኤ.ኤፍ.ዲ.) የሚባል አካል መሰረቱ። ይህ አካል በተለይም በውጭ ሀገር ትልቅ መከፋፈልን ፈጥሮ እንደነበረ ይታወሳል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከቫንኩቨር እስከ ዳላስ: ከግንቦት ሰባት እስከ ግንቦት ሀያ

 

ልጅ ተክሌ
የጳውሎስ  ማላገጥ፡ የመረራና ብሬ ቁጣ

ሕወሀት ከደርግ አምባገነን አገዛዝ ነጻ ባወጣን (ተረጋጉ፡ አልጨረስኩም)፡ እንደገና ግን ወደ ሕወሀት ቀጣይ የባሰ አምባገነንና ዘረኛ ስርአት በተሸጋገርን ባስራ ስምነተኛው ዓመት፡ ዳላስ፡ ቴክሳስ ውስጥ፡ ከዶ/ር ብርሀኑ ፊትና ጎን ተቀምጠናል። ታሪክ ማጠንጠን ጀመርን።


ሙሉውን አስነብበኝ ...