አማተሩ የአቶ መለስ ፊልምና ትውስታዎቻችን (ሀብታሙ አሰፋ)

ሀብታሙ አሰፋ (ከላስ ቬጋስ)

በኢትዮጵያ ከዛሬ አምስት ዓመት በፊት ነው። በህዝቡ ዘንድ ጎልቶ የሚደመጥ አንድ መራር ቀልድ ነበር። የአሜሪካ የስለላ ድርጅት ሲአይኤ የሩሲያው ኬጂቢ እና የኢትዮጵያው የወያኔ የስለላ ቡድን ከፌዴራል ፓሊስ ጋር ተጣምሮ ለአንድ ግዳጅ ይቀርባሉ። ግዳጁ ነብር አድሮ ማምጣት ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቻውቼስኮ እንደ መለስ፤ ኤሌና እንደ ሀዜብ

ልጅ ተክሌ - ከካናዳ

ትንቢተ ሮማኒያ፤ መልእክተ ኢትዮጵያ

1989 ዓ.ም. ነው እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠር። ታህሳስ፡ 1981 ዓ.ም. እንደ ኢትዮጵያ። በዚያ የሆነው በ20?? የሚሆነውና ያሳያል እነሆ በሮማኒያ የተከሰተውን ታሪካዊ ክስተት ማተት ፈቀድን። በዚያም ጊዜ እንዲህ ይሆናል። ከዚያ አስቀድሞ በሆነ ግዜም፤ ኒኮላ ቾቼስኮ አላደመጠም ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ92 እስከ 2002 ልደቱ አያሌው፤ እሱም አጣን እኛም አጣነው

አለቃ ተክሌ - ቫንኩቨር (ካናዳ)

ትንሽ ወደኋላ፤ የጠፉት በጎች ሲወለዱ

ጥቅምት 1992 ዓ.ም. (መሰለኝ)። አዲስ አበባ ኢትዮጵያ። ሶሰት አራት መልካቸው ያመረ፤ ወጣት፣ ሱፍ የለበሱ ቁመናቸው ብቻ ሳይሆን አቋማቸውም ጭምር የሚመሳሰል፤ ግማሹ እስላም ግማሹ ክርስቲያን፣ ግማሹ ጉራጌ ግማሹ አማራ ግን ደግሞ የሚመቹ ኢትዮጵያዊ ወጣቶች/ጎልማሶች የፖለቲካ ፓርቲ አቋቋሙ ተብሎ በሬዲዮና በቴሌቪዥን ሲነገር ከምር የወሰድናቸው አልነበርንም። ብንኖርም ብዙ አልነበርንም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተያዘው ሥራ ህዝብን ማስተባበር ወይንስ ከትግሉ ፈጽሞ ማራቅ

ፍቅሩ ይበልጣል

ሰሞኑን በሀገራችን ፖለቲካ ለሁለተኛ ጊዜ የህዝብን ቅስም የሚሰብር ድርጊት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በአንድ ወቅት የህዝብን የጋለ ስሜት አነሳስቶ የነበረውና ወደ ድል ሊያሸጋግረው ነበረው የቀድሞው ቅንጅት፣ በአመራር ላይ ባሉ ግለሰቦች አሳፋሪ የሆነ ድክመት ባልታሰበና ህዝብና ደጋፊ ባልጠበቀው ሁኔታ መንገድ ስቶ ተንኮታኩቶ ወደቀ። ያንን የወዳደቀ ስብርባሪውን አንስተው፣ ጠግነው፣ የተሰበረውን የህዝብ ልብ መልሰን ቀድሞ ወደነበረው አመኔታ እንመልሰዋለን በማለት የተነሱ ጥቂት አመራሮች እንደገና በማንሰራራት የቅንጅት ወራሽ የሆነውን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ በሚል ስያሜ በመመስረትና ልበ ሙሉዋን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን በመሪነት በመምረጥ ትግሉን ለመቀጠል ለህዝብ ቃል ገቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ነጋሶና አቶ ስየ አንድነትን ተቀላቀሉ፤ ኢትዮጵያዊነት እያሸነፈ ነው (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ (ቺካጎ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

“ኢትዮጵያውያንን እስከሆንን ድረስ ትግራይ መሬታችን ነው። ኦሮሚያ መሬታችን ነው። ደቡብ ና ሶማሊያ መሬታችን ነው። አፋርም መሬታችን ነው። ለነርሱም ትግራይ መሬታቸው ነው። አማራም ትግራይ መሬቱ ነው። ሊኖርበት ይችላል። በዚህ ማመን አለብን። ከዚህ ውጭ የፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅቶችን እንደጠላት ለማስፈራሪት መጠቀም የሥልጣን እድሜን ማራዘሚያ እንደሆነ መታወቅ አለበት። አሁንም በሰላምዊ ትግል ካመኑትና ሕጋዊ ፈቃድ ካገኙት ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር አብረን መሥራት እንቀጥላለን።” - አቶ ገብሩ አሥራት

“ኢትዮጵያ እኮ የኢህአዲግ ብቻ አይደለችም። ኢትዮጵያ የእኛም ናት” - አቶ ቡልቻ ደመቅሳ

“ኢትዮጵያችን” - ዶ/ር መራራ ጉዲና

አቶ ስየ አብርሃና ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራውን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መቀላቀላቸውን በተመለከተ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው። አስተያየቶቹ በጥቅሉ ብንመለከታቸው በሦስት ምድብ የሚከፈሉ ናቸው። የመጀመሪያው ምድብ የአብዛኛውን ኢትዮጵያዊ ስሜት ያንጸባርቃል ብዬ የማስበው፣ በአቶ ስየ አብርሃና በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ውሳኔ የተደሰቱ ኢትዮጵያውያን አስተያየቶችን የያዘ ምድብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ

ይድረስ ለጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ

ከየሺወርቅ ወንድሜነህ (የኢትዮጵያ ተወላጅ፣ የዓለም ዜጋ - በስዊድን ኗሪ)

የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ 85 ሚሊዮን ደርሷል ተብሎ ይገመታል። ከህዝቡ ወደ 57 በመቶ የሚሆነው ለመጠጥና ለምግብ መሥሪያ የሚሆን ውሃ እንኳን በመኖሪያው አካባቢ አያገኝም። ለመፀዳጃ የሚሆን ውሃ የማያገኘውማ ከመቶው 89 ይደርሳል። ከመቶው 38 ያህሉ ህዝብ ሳይጠግብ የሚያድር ደሃ ነው። ከመቶው ስምንቱ ህፃናት አምስት ዓመት ሳይሞላቸው ነው የሚሞቱት። እነዚህ ከሞላ ጎደል ተጨባጭ የሆኑ መረጃዎች ለኢትዮጵያ ህዝብ በጣም መሠረታዊ የሆኑትን ፍላጎቶቹን እንኳን የማሟላት ሁኔታ እንዳልተፈጠረለት የሚያሳዩ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መጪው ምርጫና የብርቱካን ሚደቅሳ የመፈታት መቼት?

ክርስቲያን

አብዛኛውን ጊዜ አምባገነን መሪዎች እንዴት እንደሚያስቡ ማወቅ ካባድ ነገር ነው። ባህሪያቸውን ለመተንበይ በጣም አስቸጋሪ ነው። ግን ይህንን ከባድ ነገር ለመሞከር ተነሳሁ። ብርቱካን መቼ እንደምትፈታ ለማወቅ ከመጓጓቴ ብዛት የማይደፈረውን ለመድፈር አሰብኩ። እናም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብርቱካንን መፈታት መቼ እንደሚፈቅዱ ለማወቅ ሞከርኩ። ከምርጫ በፊት ወይስ ከምርጫው በኋላ?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአቶ ስየ አብርሃና የአቶ ልደቱ አያሌው ትችቶች

“የፓርቲዎች የሥነምግባር ሕግ” በኢህአዲግና በተቃዋሚዎች መካከል መፈረሙን ተከትሎ የመድረክ መሥራች የሆኑት አቶ ስየ አብርሃ “ሥነምግባር ሲሉ …” በሚል ርዕስ ሀገር ቤት በሚታተመው “አዲስ ነገር” ጋዜጣ ላይ ኅዳር 5 ቀን 2002 ዓ.ም. ዕትም ላይ አስተያየት ሰጥተው ነበር። የአቶ ስየን አስተያየት አስመልክቶ አቶ ልደቱ አያሌው ደግሞ “እነ አቶ ስየና የስምምነት ጥላቻቸው፤ ‘አርባ ዓመት ውቅያኖስ ውስጥ የኖረ አለት መዋኘት አይለምድም’ …” በሚል ምላሽ ሰጥተዋቸዋል። የሁለቱንም ወገኖች አስተያየት ለአንባብያን ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ አቅርበነዋል። መልካም ንባብ!!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከሳጥን ውጭ ማሰብ አይከፋም (ኩችዬ)

Hailu Shawel shaking hands with Meles Zenawi (ስለ ኃይሉ፣ ኢህአዴግ፣ ፈረንጆቹና ብርቱካን)

ኩችዬ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ብርድ ልብስ ውስጥ እንደተጀበንኩ የኢትዮጵያን ፖለቲካ መፍታት ሲሳነኝ የቡና ተርቲበኛ ወዳጄን “ካሪቡ” እንደምቀጥረው አምና አካባቢ ያጫወትኳችሁ መሰለኝ። እጣኑ ይጐድል እንደሁ እንጅ የካሪቡ ቡናና የቤቱ ጌጥ (ፌንክ-ሹዌ ይሉታል ቻይናዎች) ከራማ ያስታርቃል። ታዲያ ይሄ ወዳጄ አንገቱን ከብርድ ልብስ ውስጥ ብቅ አርጎ መወያየትን አይፈራም። ጥልቅ አሳቢነቱን ብቻ ሳይሆን ወዛም ጨዋታውንም እናፍቀዋለሁ። እንዲህ ያለ ወዳጅ አያሳጣችሁ አቦ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...