በክፍፍል የሚታመሰው የተቃዋሚዎች መንደር (ጽዮን ግርማ)

የፓርቲዎች አመራሮች ስለ ክፍፍሉ ይናገራሉ

ጽዮን ግርማ

ከተመሠረተ በአንድ ዓመቱ የመሰንጠቅ አደጋ ያንዣበበትን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፤ እንዲሁም በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የነበሩና ያሉ ፓርቲዎችን በአንድነትና በሕብረት መሥራትና መጓዝ ያለመቻላቸውን አባዜ አስመልክቶ ጋዜጠና ጽዮን ግርማ በጉዳዩ ላይ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያምን፣ ኢንጂንየር ግዛቸው ሽፈራውን፣ የፖለቲካ ምሁራንን፣ አቶ ገብሩ አስራትን፣ አቶ ስዬ አብርሃን እና ሌሎች ወገኖችን በማነጋገር ያቀረበችው ጽሑፍ ነው። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ጴጥሮስ ያቺን” ቃል (መክብብ ማሞ)

Abune Petros አቡነ ጴጥሮስ መክብብ ማሞ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

”ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሉዋቸው እውነት እንዳይመስላችሁ። ሽፍታ ማለት ያለ ሀገሩ መጥቶ የሰውን ሀገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው። የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን!” አቡነ ጴጥሮስ።

ያለፈው ረቡዕ ሐምሌ 22 ቀን ጀግናው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በግፍ የተገደሉበት 73ኛ ዓመት ነበር። እኒህ ታላቅ አባት ለሰማዕትነት ያበቃቸው ዋናው ምክንያት በወቅቱ ለተጠየቁት ቀላል ለሚመስል ጥያቄ፤ ”ቃሌን አልክድም” ብለው በመቆማቸው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የኢትዮጵያና ኤርትራ ፌዴሬሽን አስፈላጊነት” ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ

Administrative Mapበካሊፎርኒያ ሳን ዮሴ ባለፈው ግንቦት 7 ቀን 2001 ዓ.ም. በተካሄደው የኢትዮጵያውያንና የኤርትራውያን የወዳጅነት ኮንፈረንስ ላይ ፕ/ር ተስፋጽዮን መድኅኔ እና ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ ተናጋሪዎች እንደነበሩ መዘገባችን አይዘነጋም። “የኢትዮጵያንና የኤርትራን ወንድማማች ህዝቦች ሊቀራርብ የሚችለው የኮንፌዴሬሽን ሥርዓት ነው” በማለት ፕ/ር ተስፋጽዮን መድኅኔ ”ኢትዮጵያና ኤርትራ ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ባቀረቡትን ጽሑፍ አስነብበን የፕ/ር ዳንኤል ክንዴን ጽሑፍ ለማቅረብ ቃል ገብተን ነበር። ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ “የኢትዮጵያና ኤርትራ ፌዴሬሽን አስፈላጊነት” በሚል ርዕስ ያቀረቡትን ጽሑፍ ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደሴ ህዝብ - ተረኛው የመስዋዕትነት ጠቦት? (መሣፍንት)

መሣፍንት ዘፈረንሣይ ለጋሲዮን (አዲስ አበባ) ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ሐምሌ 2001 ዓ.ም.

ከሣምንታት በፊት ያደመጥኩት አንድ ዜና በርካታ ነገሮችን ወደ አዕምሮዬ እያመላለሰና ከዚህ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት በውስጤ እየፈጠረ ፋታ ሲነሳኝ ይህችን ወረቀት ጫጭሬ የተሰማኝን ለወገኖቼ ባካፍልስ ብዬ አሰብኩና ብዕሬን አነሳሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌስቲቫል 2009 ግምገማ (ክንፉ አሰፋ)

ክንፉ አሰፋ 3 August 2009

Pairs Ethio-Festival 2009"... ከሁለቱ የመጫወቻ ሜዳዎች ትይዩ ባለች አንድ ዛፍ ጥላ ስር በርጫና ሽሻው ሞቅ ብሏል። ለየት ባለ መልኩ “ለመዝናናት የመጡ” ወጣቶች ሕይወታቸውን ይቀጫሉ። ጫትን በግልጽ መቃምም ሆነ መሸጥ አይከለከልም። “ኢትዮጵያም አይከለከልም” ያለኝ ወዳጄን አልረሳውም። “ይህ የኢትዮጵያን ባህልም የምናንጸባርቅበት መድረክ ነው። ሀገራችን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም በግልጽ ነው የሚቅመው።” ነበር ያለው። እውነቱን'ኮ ነው። ለኳስ ከመጣው ለጫት የመጣው ይበልጥ ነበር። በዚሁ ከቀጠለ በቅርብ ጊዜ የስፖርቱ ፌዴሬሽን - የአውሮፓ የጫትና ሺሻ ፌዴሬሽን የማይሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም። ..." በማለት በፓሪስ የተካሄደውን በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫልን የገመገመው ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለሱማሌ መፍትሔ የአራትዮሽ ውይይት መጀመር ያስፈልጋል

ዳኮታ የጥናት ማዕከል

(አልሽባብ፤ ኢትዮጵያዊ ኃይል፤ የኤርትራና የአሜሪካ መንግሥት)

ሱማሌ የአልሽባብ ተዋጊዎች 98%፤ እነመለስና አሜሪካኖች ሊያቆሙት የሚፈልጉት መንግሥት ሁለት በመቶውን የሱማሌ ግዛት ተቆጣጥሮ ነው ያለው። መንግሥት ተብዬው እራሱን ከአልሽባብ ታጋዮች ከመከላከል በስተቀር ለማጥቃትና ይዞታውን ለማስፋፋት ምንም አቅም የለውም። እስከጭራሹም ሱማሌን ለቆ እንዲወጣ ቀነ ቀጠሮ እየተቆረጠለት ነው ያለው። የበዙት የህዝብ ተወካዮች፤ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ወደተለያየ ሀገር ጥለው ፈርጥጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብሔራዊ ተጠያቂነት ያልከበደው የአንድነት አታካራ (ስሜነህ)

“… የእኛን መለያየት ልዩ የሚያደርገው በሃሳብ ከእኛ የተለየን የራሳችንን ወገን ከምድረ ገጽ ድራሹን ካላጠፋንና ሞራሉን አንኮታኩተን እርኩሳዊ እርካታን ካላገኘን እንቅልፍ ያለመተኛታችን አባዜ ነው። ወይ እኛ አንተኛ ወይ ሰው አናስተኛ። ግራ የገባን፣ ቀናነት የጎደለን፣ … ህዝቦች። የተለያዩ ልምዶችም ሆኑ የ2 ሺህ ዓመት ሚሊኒየም ምንም ያላስተማሩን። …” የሚሉት በስዊድን የቀድሞ ቅንጅት በኋላም የአንድነት የድጋፍ ሰጪ ማኅበር ዋና ፀሐፊ የነበሩት አቶ ስሜነህ ታምራት ናቸው። አቶ ስሜነህ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ የሰጡትን ጠንከር ያለ አስተያየት ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ እንዲህ ሊያናቁር ይገባል? (ኩችዬ)

ኩችዬ - ሐምሌ 24 ቀን 2001 ዓ.ም July 31, 2009 www.kuchiye.blogspot.com  

በአንድነት ፓርቲ ዙሪያ የሚናፈሰው ውዝግብ ወርደ-ሰፊ ትምህርት ያዘለ ነው። ትምህርቱ ለፓርቲው ኃላፊዎችና ደጋፊዎች ብቻ ባድራሻ የተላከ ሳይሆን፤ ባገራቸው ፖለቲካ ሕይወት ውስጥ ሁነኛ ለውጥ እናመጣለን ብለው ለሚባዝኑ ሌሎች ፓርቲዎች ጭምር የሚተርፍ መልካም ትምህርት ነው። ከዲስኩር ላድናችሁ ብዬ ነው እንጂ በዚህ ዙሪያ ብዙ የምለው ነበረኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ሰሞኑን በተፈጠሩ ክስተቶች ላይ (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ሐምሌ 22 ቀን 2001 ዓ.ም.

በአንድነት ውስጥ የተነሳው ውዝግብ የአንድነትን ጥንካሬን የሚያሳይ ነው!

ሰሞኑን በአንድነት ውስጥ ተፈጠረ የተባለውን ውዝግብ በተለይም አፍቃሪ ኢህአዲግ ድረ ገጾች ሎተሪ የወጣላቸው ይመስል ሲያራግቡትና ሲያሟሙቁት ሰንብተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወደ ራሴ ስመለከት - እንደ እኔ ላለ ዲሞክራሲ፣ ነፃነትና ሀገር አይገባውም (ዳኛቸው ቢ.)

ዳኛቸው ቢያድግልኝ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

ብዙ ተቺዎች ወይም ሃያሲዎች ወቃሾችና ከሳሾች ባሉበት ሀገር ታታሪና ትጉህ ሰራተኞች ጥቂት ናቸው። ጣት መጠንቆል ቀርቶ ወደራስ መመልከት ተገቢ የሆነበት ደረጃ ላይ በመድረሳችን “ሌሎች ምን?” ሠሩ ሳይሆን፤ “እኔ ምን ስለሠራሁ ነው ፍትህ፣ ነፃነት ሀገርና ዲሞክራሲ ይገባኛል ማለት የምችለው?” የሚለው ጥያቄ በነፍስ ወከፍ መመለስ ያለበት ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...