እንሆ የእርቅ ሃሳብ (ግርማ ካሣ)

የምርጫው ውዝግብ ቀጠሏል - የሚያዳምጥ ካለ እንሆ የእርቅ ሃሳብ

ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ግንቦት 18 ቀን 2002 ዓ.ም.

ምርጫ 2002 ከተደረገ አራት ቀናት ሆኑት። ገዢው ፓርቲ ዘጠና ዘጠኝ በመቶ አሸናፊ ነኝ ብሎ አወጀ። የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢ ቡድን ምርጫው የአለም አቀፍ መስፈርትን ያሟላ እንዳልሆነ ይፋ አደረገ። የአሜሪካ መንግስት ምርጫው ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ እንዳልሆነ የሚገልጽ መግለጫ አወጣ። ቢቢሲ፣ አሶስየትድ ፕሬሥ፣ ሮየርትስ፣ ቪኦዔ፣ አጃንስ ፍራንስ ፕሬሥ፣ ዋሺንግተን ፖስት …ምርጫውን እንደተጭበረበረ በሰፊው እያተቱ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሃምሳ አለቃ ደሳለኝ (ቴድሮስ ኃይለ)

ቴድሮስ ኃይለ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ከደርጉ የገበሬ ማኅበር ካድሬዎች በገራገርነቱ የሚታወቀው የጎጃሙ ቆምጫምባው እንደዋዛ አለ ተብሎ ከሚነገርለት አባባል አንዱ፤ ጋዜጠኛ ”ለመሆኑ ክቡርነትዎ የአሜሪካንን ኢምፔሪያሊዝም እንዴት ይመለከቱታል?” ሲል ለጠየቃቸው፤ ጓድነታቸው ባልተንዛዛ አማርኛ ”የጎሪጥ ነው የማየው” ሲሉ ቆፍጠን ያለ መልስ እንደሰጡ በቀልድ መልክ ሲነገርና፤ ለአንዳንድ ግልገል ካድሬዎችና አድርባዮችም ጭፍን አቋምና ባዶ ፕሮፓጋንዳ እንደ ምሳሌ ሲቀርብ ይስተዋላል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

0.6% ያገኙት ተቃዋሚዎች ናቸው ህወሓትን ያሸነፉት

0.6% ያገኙት፣ ግን 99.4% ያገኘውን ህወሓትን ያሸነፉት ተቃዋሚዎች ናቸው

ናኦሚ በጋሻው ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

”ምርጫ” ተደረገ ይሉናል። እኛ ግን ጨዋታና ቀልድ ነው የተደረገው እንላለን። ከምርጫው በፊት ይሄንኑ ነበር የምንናገረው። ምርጫ የሚወሰነው በድምፅ ሰጪው ሳይሆን በቆጣሪው ነው ስንል ነበር። መድረኩ ”ተሸነፈ” እንደሚባል ጥርጣሬ አልነበረንም። እንደገመትነውም እንደ ዶር መርራ ጉዲና፣ ኢንጂነር ግዛቸው፣ አቶ አንዱዋለም፣ አቶ ስየ አብርሃ የመሳሰሉ አንጋፋና ተወዳጅ የፖለቲካ መሪዎች፣ ተሸነፉ እየተባልን ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግልጽ ደብዳቤ - ለአቶ መለስ ዜናዊ

ይድረስ ለተከበሩ አቶ መለስ ዜናዊ

ተጻፈ ከግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

ምድረ አሜሪካ - ቺካጎ

በቅድሚያ ባሉበት ቦታ ለርስዎና ለቤተሰብዎ ሠላምታዬ ይድረስዎ!

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ፣ አምላክ ሆኖ ሳለ እኛን ለማዳን ወደዚች ምድር መጣ። ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ ወንድ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ተወልዶ ሰው ሆነ። በምድር በሚመላለስበት ጊዜ እራሱን ሲጠራ ”የሰው ልጅ” ብሎ ነበር የሚጠራው። በመስቀል ላይ በነበረበት ወቅትም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አንዱ ደቀ መዝሙሩን ሲያለቅሱ አይቶ፣ እናቱን ”አንቺ ሴት እንሆ ልጅሽ” ነበር ያላት። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግልጽ ደብዳቤ ለአቶ መለስ ዜናዊ፣ ለአቡነ ጳውሎስ፣ ...

ከኮሎኔል አሥራት ቦጋለ

1. ለአቶ መለስ ዜናዊ እና ለወያኔ ድርጅት፣

2. ለአቡነ ጳውሎስ፣

3. በየጊዜው ከሚነፍሰው ነፋስ ጋር ለምትነፍሱ ብሌጣ-ብልጥ ሆድ-አደሮች፣

4. ለተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ድርጅቶች፣

5. ለመለዮ ለባሹ ሠራዊት፣

6. ለኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ፣

ከሁሉ በማስቀደም በየአቅጣጫው ሁላችሁንም ከሚያጋጥማችሁ ስህተቶች እየተገታችሁ ወደ ቁምነገር በመመለስ በጎ በጎውን እንዲያሳስባችሁ እመኝላችኋለሁ። እውነት እንደሬት የምትመር እንደ ኮሶ የምታንገፈግፍ ስለሆነች ብዙ ጊዜ አቅራቢያዎቿን ትሰዋለች። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምርጫ ዋዜማ እንዲህ አለፈ… (እይታ- ከአዲስ አበባ)

ከአዲስ አበባ ወደ የክ/ሀገሩ ሸቀጣ ሸቀጦችን የሚያስጭኑ ነጋዴዎች ሥራቸውን አቁመዋል። በባንክ የነበራቸውን ገንዘብ በማውጣት በየቤታቸው አስቀምጠዋል። ምክንያቱ ከምርጫው ጋር በተያያዘ ችግር ቢፈጠር ቅድሚያ ጥንቃቄ ለማድረግ ነው። አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ከምርጫው ጋር በተያየዘ የአንዳንድ ተማሪዎችን የፈተና ጊዜ አራዝሟል። በዚህና ይሄን በመሰለው ምክንያት የ6ኪሎ ዩንቨርስቲ ምድረ-ግቢ ከሐሙስ ጀምሮ ፀጥ-ረጭ ብሏል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድርጅታዊ አቅም ሳይገነቡ ስሜታዊ እርምጃዎች መውሰድ ጉዳት አለው

ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

በቅርቡ «ምርጫው ቀልድ ነው፤ መድረኩ ግን ቢሳተፍ ይበጀዋል» በሚል ርእስ ለአንባቢያን ባቀረብኩት ጽሁፍ ላይ ባነሳኋቸው አንዳንድ ነጥቦች ላይ፣ የማውቃቸውና የማክበራቸው ወዳጄ፣ አቶ ይልማ በቀለ የሰጡትን ምላሽ አነበብኩ። አቶ ይልማ በተለያዩ የአገራችን ጉዳዮች ላይ ትምህርት ሰጪ መጣጥፍት የሚያቀርቡ ጠንካራ ኢትዮጵያዊ የዲሞክራሲ ታጋይ ናቸው። በዚህ አጋጣሚ ለሚያደርጉት አስተዋጾና ጥረት ላመሰግናቸው እወዳለሁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫውን አለመሳተፉ ጥቅም ላያመጣ ቢችልም ትልቅ ጉዳት ግን ይኖረዋል

ናኦሚ በጋሻው ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

“ምርጫ ቀልድ ነው። መድረኩ ግን መሳተፉ ይበጀዋል” በሚል ርዕስ አቶ ግርማ ካሣ የጻፉትን መጣጥፍ ኢትዮሜዲያ ላይ ወጥቶ አነበበኩ። ርዕስ አመራረጣቸው የሚያስደንቅ ነው። ርዕሱን በመመልከት “ምን ማለታቸው ነው? ቀልድ ነው ብለው እንዴት ተሳተፉ ይላሉ” ብዬ ወዲያው ነበር ጽሑፉቸውን ያነበብኩት። ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ ከቀልዱ ምርጫ ራሱን በማግለል፤ ቁም ነገር ይሥራ

ሀብታሙ አሰፋ

ምርጫ 2002 አስቀድሞ በሂደቱ ተጭበርብሮ የቀረው የመጨረሻ ቀን ቴአትር ብቻ ነው። የቴአትሩ አዘጋጆች እና መሪ ተዋንያኑ የእነ አቶ መለስ ቡድን ያሰበው እንዲሳካ መታጀብ ይፈልጋል። የዚህ የተጭበረበረ ሂደት ውጤታማ እንዲሆን ላለፉት አምስት ዓመታት ሕገ ወጥ ሥራዎችን ሠርቷል። በዚህም ቀዳዳዎችን ሁሉ ደፍኜያለሁ ብሎ ይናገራል። ተደጋግሞ እንደተገለጸው የተደፈኑት ቀዳዳዎች የአፈና ሥርዓቱን በሥልጣን ለማቆየት የወጡ ሕገ ወጥ አዋጆችና ልዩ ልዩ እርምጃዎች ናቸው። አሸባሪው ”የፀረ-አሸባሪነት” አዋጅ ይቃወሙኛል ያላቸውን ሁሉ ለማፈን እየዋለ ነው። የፕሬስ ነፃነትን አደጋ ላይ ጥሏል። የአዲስ ነገር አዘጋጆችን መጨረሻ ልብ ይሏል። የነ ጄኔራል ተፈራ ማሞን የፈጠራ ክስ እና ሕገ ወጥ ውሳኔ ማንሳት ይበቃል። ምርጫውን በፈለገው መንገድ ለመቆጣጠር እንዲችል የሀገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢ ጠንካራ ተቃዋሚ እንዳይኖር የተቻለውን ሁሉ አድርጓል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቀልድ ምርጫ መሳተፍ ትርጉሙ ምንድነው?

ይልማ በቀለ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

ውድ ወንድሜ አቶ ግርማ ካሣ ያቀረቡትን ጽሑፍ በአዲስ ቮይስ ድረ ገጽ ላይ አንብቤዋለሁ። አቶ ግርማ ካሣ በየጊዜው በዳያስፖራ ድረ ገፆች ላይ በአለው የሀገራችን ሁኔታ የሚጽፉትን ተከታትዬ አነበዋለሁ። ጊዜዎትን ወስደው፤ በጥሞና አስበው የሚያወጡት ጽሑፍ አንባቢዎች ስለ ውድ ሀገራችን እንድናስብ ያበረታታናል ብዬ አምናለሁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...